የግብፅ የ ጦር አዛዥ የምርጫ ዝግጅት

የግብፅ የጦር ኃይል አዛዥ አበደል ፈታህ አል ሲሲ የወታደራዊ የደንብ ልብሳቸዉን በይፋ የሚቀይሩበት ጊዜ ተቃርቧል። ትናንት ነዉ የጦር አዛዡ ከመከላከያ ሚኒስትርነታቸዉ በይፋ በመልቀቅ ለፕሬዝደንትነት ለመወዳደር መወሰናቸዉን ያስታወቁት።