ሽሽት ከናይጀሪያው ቦኮሃራም

በርካታ ናይጀሪያውያን ቦኮሃራም የሚያደርሰውን ጥቃት በመሸሽ እየተሰደዱ ነው ። አብዛኛዎቹ የሚፈናቀሉት በተለይ ባለፈው ዓመት በግንቦት ወር መንግሥት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከደነገገባቸው ከሰሜን ምሥራቅ ናይጀሪያ ግዛቶች ነው ። በዚህ ሰበብ የሃገር ውስጥ ተፈናቃዮች ቁጥር እየጨመረ መሄድ በተለይ በትላልቅ ከተሞች አሉታዊ ተፅእኖ አሳድሯል ።