አቡጊዳ – የአቶ አለምነህ አስተባበሉ ፤ ግን የኦዲዮ በማስረጃ አለ!

አቶ አልምነው መኮንን በ«አማራዉ» ላይ በተናገሩት የንቀት አባባሎች ምክንያት፣ ባለስልጣኑ ከሃላፊነታቸው እንዲነሱና ለፍርድ እንዲቀርቡ፣ አንድነት እና መኢአድ በመጠየቅ የክልሉ መስተዳደር በሚገኝበት በባህር ዳር ከተማ እሁድ የካቲት 16 ቀን ሰላማዊ ሰልፍ መጠራቱ ይታወቃል።

በባህር ዳር ቅስቀሳው እየተፋፋመ ባለበት ወቅት፣ አቶ አልምነዉ መኮንን ማስተባበያ በኢቲቪ እየተላለፈ መሆኑ የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት ፌስቡክ የሚሊየነሞች ድምጽ ለነጻነት ፌስ ቡክ ፔጅ ከታች እንደተገለጸው ዘግቧል። በቀጥታ በፌስቡክ የሚሊየምን ድምጽ ለነጻነት የሚያደርጋቸውን እንቅስቃሴ ለመከታተል እዚህ ይጫኑ !

======================
በባህር ዳር ቅስቀሳው ተፋፍሟል። በዉጭ አገር የሚገኙ ታዋቂ ድህረ ገጾችና ሜዲያዎችም ከፍተኛ ትብብር እያደረጉ ነዉ። ዘሃበሻ፣ ኢትዮጵያን ሪቪዉ፣ ኢ.ኤም.ኤፍ፣ ኢሳት፣ አቡጊዳ በባህር ዳር በስፋት እየዘገቡት ነዉ። የብአዴን/ኢሕአዴግ አመራሮች የክልሉን ጥቅም የሚያስጠብቁ፣ ሕዝቡን የሚያከብሩ ሳይሆን ፣ ሕዝቡን የሚንቁና ከሕዝቡ ጋር የተጣሉ መሆናቸው ለብዙዎች እንግዳ አይደለም። አማርኛ ተናጋሪዎች ከሌሎች ክልሎች በግፍ ሲባረሩ፣ የክልሉ መሬት ለሱዳን ሲሰጥ፣ ዝምታን የመረጡ ናቸው።

ይግረም ተብሎ፣ በገሃድ በፊት ለፊት ሕዝቡን ሲያዋርዱ፣ ሲሰድቡ እየሰማናቸው ነው። ይህ «አማራዉ» ላይ የተሰነዘረው የንቀት ንግግር፣ በማስረጃ የተረጋገጠ ነው።

የብአዴኑ/ኢሕአዴግ መሪ «አማራ» በሚባለው ማህበረሰብ ላይ የሰጡትን አስተያየት ለማዳመጥ እዚህ ይጫኑ !