አቡጊዳ – ሰማያዊ ፓርቲ የጠራዉ የጎንደር ሰላማዊ ሰልፍ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ !

በከፍተኛ ወከባ ዉስጥ ቢኮንም፣ የሰማያዊ ፓርቲ የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ በጎንደር መስቀል አደበባይ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን ዘገባዎች ገለጹ። የኢትዮ-ሱዳን ድንበርን በተመለከተ የተጠራው ሰልፍ ፣ ከበላይ በተሰጠ ትእዛዝ መሰረት፣ ፖሊሶች መንገዶችን እየዘጉ ሕዝብ እንዳይቀላቀል ቢያደርጉም፣ በርካታ ሕዝብ፣ የነበሩ መሰናክሎችን ሁሉ እያለፈ፣ በሰልፉ ተገኝቷል።

«ተከበርሽ የኖርሽው ባባቶቻችን ደም ፣ እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይወደም» እያሉ ሰልፈኞች በመዘፈን በአገር ዳር ድንበር ጉዳይ ቀልድ እንደሌላ ያሳወቁት።

ይህ ሰማያዊ ፓርቲ የጠራዉ ሰልፍ በጎንደር ሁለተኛው ሰልፍ መሆኑ ነዉ። ከአራት ወራት በፊት በሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት እንቅስቃሴ ዘመቻ ወቅት፣ የአንድነት ፓርቲ በጠራው ሰልፍ ከ40 ሺሆች በላይ መስቀል አደባባይን ማጥለቅለቃቸው የሚታወቅ ነዉ።

ሚኒሊክ ሳልሳዊ በስፋት የዘገበዉን ለማንበብ እዚህ ጋር ይጫኑ !