An interesting article. (NB. Not mine)

«…………………………….ሴንት ሉስ እያለሁ በጣም የማከብራቸው የኮፕቲክ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ Father Baslios
የሚባሉ ቄስ ነበሩ። ከእለታት አንድ ቀን ልጎበኛቸው ከመኖሪያ ቤታቸው ሄድኩ። በተቀመጥቁበት ወንበር ሆኜ በፊቴ ያለውን
ጠረጴዛ ስመለከት በጠረጴዛው ላይ በአረበኛ እና በእንግሊዘኛ ዓረብ አገር ተዘጋጅቶ የተላከላቸውን መጽሄቶች ሳገላብጥ፤
እሳቸው አዩኝና “የራስህ አገር መንግሥት የሚያደርገውን በውስጡ ታገኛለህ” አሉኛ፤ ውስጡን ሳገላብጥ እነ አቶ መለሰ
ያደረጉትን ደባ ተጽፎ አነበብኩ።

ታሪኩ እንደዚህ ነው፤ እነ አቶ መለሰ ከኢትዮጵያ ጋራ በሚዋጉበት ወቅት “በናንተ ሙሉ እርዳታ አሸንፈን ኢትዮጵያን
ከተቆጣጠርን ኢትዮጵያን የዓረብ ሊግ አባል የምትሆንበትን ህግ አውጥተን እናውጃለን” እያሉ ለዓረቡ ዓለም ቃል ገብተው
ኖሮ፤ እንደተመኙት ሆነላቸው እና፤ እንደገቡ ያውጃሉ ብለው እነ አቶ መለሰን ቢጠብቍ ዘገዩ ባቸው። “ለምን ዘገያችሁ ?
ብለው እነ አቶ መለሰን ዓረቦች ጠየቋቸው።

እነ አቶ መለሰ የሰጧቸው መልስ “በአገር አንድነት ህዝቡን አስተሳስራ የኖረችውን ቤተ ክርስቲያን ሳናዳክማት፤ በብሄራዊ
ወኔ ያስተሳሰረችውንም ህዝብ በመከፋፈል ኃይሉን ሳናፈርሰው ልናውጅ ብንሞክር ለህልውናችን አዳጋች ስለሆነ ጊዜ ስጡን፤
ይልቁን በኢትዮጵያ ያሉት ሙስሊሞች ባለፈው መንግስት እየተገደድን የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ መቅደስን ህንጻ ሰርተናልና
እኛም ገብተን እንጸልይ እንዲሉ ግፏቸው። እኛም መብታቸው ነው በማለት እስከ በመፍቀድ ድረስ እንገፋለን። በዚህ ሁኔታ ቤተ
ክርስቲያንንም ህዝቡንም ካዳከምን በኋል እናውጃለን እንጅ፤ አሁን ብናውጅ እንዳሰብነው አይሆንም” ብለው መልስ እንደሰጧቸው
ይገልጻል። ዓረቦች ይህን ታግሰው ከመቀበል ይልቅ በጣም ቸኮሉና፤ እነ አቶ መለሰን ለመርዳት ታጥቀው የሚገቡበትን መንገድ
ተሰብስበው ሲነጋገሩ፤ ያካባቢው ሽማግሎች “ነብያችን ሀበሾች እውነተኛ የመሲህ ሰዎች ናቸው እና እንዳትነኳቸው ብለው
አዝዘውናል። ቀን ጥሏቸዋል ብለን ይህን የመሰለ ደባ በአበሾች ላይ መፈጸም ከአላህ ጋራ መጋጨት ነውና አቁሙ” አሏቸው።

እነ አቶ መለሰን ለመርዳት ታጥቀው ለመግባት የፈለጉት ዓረቦች “አሁን በኢትዮጵያ ምድር ያለው አበሻ በነቢዩ ዘመን
እንደነበሩት የመሲህ ሰዎች አይደሉም። ወደ ፈጣሪ አልባ እምነት ተለውጠዋል። ግማሹ በመስቀል ጦርነት ጊዜ ወደወረረን
ክርስትና የተገለበጡ ናቸው ብለው እነ መለሰ ነግረውናል” ብለው እንደመለሱላቸው እና፤ ሽማግሎችም ”ምንም ይሁኑ በሀበሻ
ምድር ላይ ካሉ እንዳትነኩ” ብለው አስቆሟቸው” የሚል በመጽሄቱ ላይ ተመዝግቦ አነበብኩ።

ኢትዮጵያውያን ሆይ! መጀመሪያ “ከረድችሁን እና አሸንፈን ኢትዮጵያን ከተቆጣጠርን ኢትዮጵያን የዓረብ ሊግ አባል
የምትሆንበትን ህግ አውጥተን እናውጃለን”ማለታቸውን፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ “በአገር አንድነት ህዝቡን አስተሳስራ የኖረችውን ቤተ
ክርስቲያን ሳናዳክማት፤ በብሄራዊ ወኔ ያስተሳሰረችውንም ህዝብ በመከፋፈል ኃይሉን ሳናፈርሰው ልናውጅ ብንሞክር ለህልውናችን
አዳጋች ስለሆነ ጊዜ ስጡን ማለታቸውን፤እስከዚያ ግን የኛን እቅድ በማራመድ እንዲረዱን በአገራችን ያሉት ሙስሊሞችን
በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ መቅደስ እኛም ገብተን እንጸልይ እንዲሉ ግፏቸው” ማለታቸውን ስንመለከት፤ የዓረቡን ዓልም ሳይቀር
በማታለል ኢትዮጵያን ለማፍረስ እነ አቶ መለሰ ያለ የሌለ አራዊታዊ ባህርያቸውን በግልጽ እንረዳለን። በበኩሌ ይህ
እየዘገነነኝ ሳለ፤ አሁን በቅርቡ ደግሞ እነ አቶ መለሰ የዘረጉትን ህገ አራዊት ዶክተር አረጋዊ በርሄ፦

*“**የትግራይ* *ህዝብ* *ነጻ* *አውጭ* *ግንባር* *በ**1979 **አመተ* *ምህረት* *አስተሳሰብ* *ለዋጭ*
*የፕሮፓጋንዳ* *መርሀ* *ግብር* *ለሚመለምላቸው* *ቀሳውስት* *ዘረጋ።* *የማሰልጠኑ* *ዓላማ* *ቤተ*
*ክርስቲያኗን* *ከህዝብ* *ለይቶ* *በመምታት* *ስፋቷን* *ማጥበብና* *በትግሬአዊነት* *ላይ* *ብቻ* *የተመሰረተ*
*ስሜት* *በትግራይ* *ተወላጆች* *ጭንቅላት* *መክተት* *ነው።* *ቤተ* *ክርስቲያኗ* *ለረዥም* *ዘመናት*
*በህዝቡ* *አዕምሮ* *ላይ* *ስትተቀርጸው* *የኖረችውን* *ብሄራዊ* *የኢትዮጵያነትን* *ስሜት* *ከትግራይ* *ህዝብ*
*አዕምሮ* *ጠራርጎ* *በጠባቡ* *ትግሬአዊነት* *ስሜት* *በመተካት* *የቤተ* *ክርስቲያኒቱን* *ይዘት* *እያጠበቡ*
*ራሷን* *ቤተ* *ክርስቲያኒቱን* *መምታት* *ነው**”* ብለው የገለጹትን ጽሁፍ አግኝቸ አነበብኩ። ታዲይ የኔ ቢጤ
የቆሎ ተማሪ ጭንቅላት እንደሰረዝ ቅኔ የተደራረበውን የነ ገብረ ኪዳን ደስታን ህገ አራዊት እንዴት እና በምን መንገድ
ሊገልጸው ይችላል?

በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ መነኮሳትና ሰባኪዎች መስለው ሰርገው ገብተው የነገብረ ኪዳንን አራዊታዊ ተልኮ የሚያራምዱትን
በግልጽ እስካየሁ እና የዶ ክተር አረጋዊ በርሄን ጽሁፍ አግኝቼ በማንበብ እስካረጋገጥኩ ድረስ፤ በኮፕቲክ ቤተ ክርስቲያን
ካገኘሁት መጽሄት ያነበብኩት ሰመመን ይሁን ይሁንብኝ እንጅ፤ በጣም አልከከነኝም ነበር።