አቡጊዳ – ሰማያዊ ጥር 25 ቀን በጎንደር ሰልፍ ጠራ
«አባቶቻችን በደምና በጥንታቸው ገትረው ያቆዩልንን መሬት ስንዝር አናሳልፍም» በሚል መርህ የሰማያዊ ፓርቲ በጎንደ ከተማ ታላቅ የተቃዉሞ ሰልፍ ጠርቷል።

ሰልፉ የሚደረገዉ እሁድ ጥር 25 ቀን ሲሆን፣ ቦታውም በጎንደር መስቀል አደባባይ እንደሚሆን የሰማያዊ መግለጫ ይጠቁማል።
ሰማያዊ ሌሎች የሲቪክ ማህበራት እና የፖለቲካ ድርጅቶ እንዲተባበሩ ጥሪ ያቀረበ ሲሆን፣ የአደባባይ ጥሪ ከማስተልለፍ ባሻገር፣ ምን ያህል ግን ሰልፉን በጋራ ለማቀናጀት ከሌሎች ጋር ንግግር እያደረገ እንደሆነ የሚታወቅ ነገር የልም።