የአውሮፓ ህብረትና የጀርመን የአፍሪቃ ወታደራዊ ተልዕኮ

የአውሮፓ ህብረት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ትናንት ብራሰልስ ቤልጅየም ውስጥ ባካሄዱት ስብሰባ በማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ የሚካሄደውን ግጭት ለማስቆም የሚያግዙ ወታደሮችን ለመላክ ተስማምተዋል ። የአውሮፓ ህብረት የማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ ዘመቻና የጀርመን የአፍሪቃ ወታደራዊ ተልዕኮ የዛሬው አውሮፓ ና ጀርመን ዝግጅታች ትኩረት ነው ።