የደቡብ ሱዳኖች የሰላም ንግግር

የማቻርና የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር ተደራዳሪ ልዑካኖች አዲስ አበባ ውስጥ በተናጠል ከሸምጋዩ ከምሥራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግሥታት በእንግሊዘኛው ምህፃር IGAD ጋር እየተነጋገሩ ነው ። ቀጥተኛው ወይም የፊት ለፊቱ ንግግር ደግሞ ነገ ወይም ከነገ ወዲያ ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል ።