የኢትዮጵያዉያን ሁኔታ በሳዑዲ

በስዑድ አረቢያ ወደ80 ሺህ የሚገመቱ ኢትዮጵያዉያን እጃቸዉን በሰላም እየሰጡ ወደሀገራቸዉ እንዲመለሱ መጠየቁ እየተነገረ ነዉ። ከጄዳ ቆንስላ እንደተነገረ የተጠቀሰዉን ማሳሰቢያ አስመልክቶ ማብራሪያ እንዲሰጡን ወደቆንስላዉ ባለስልጣናት ያደረግነዉ ተደጋጋሚ የስልክ ጥሪ ምላሽ አላገኘም።