የኔልሰን ማንዴላ መታሰቢያ በዋሽንግተን ዲሲው ብሄራዊ ካቴድራል

ባለፈው ሳምንት ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት የደቡብ አፍሪካው የጸረ-ዓፓርታይድ እንቅስቃሴ መሪና የነጻነት አባት ኔልሰን ማንዴላ እዚህ ዋሽንግተን ዲሲ ውስጥ በዛሬው እለት በተካሄደ የጸሎት ስነ ስርዓት ታስበዋል።

በብሄራዊ ካቴድራል በተካሄደው በዚህ ሥነ ሥርዓት የዩናይትድ ስቴትስ ምክትል ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን፥ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፥ የኮንግረስ አባላትና ዲፕሎማቶች፤ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።