የአቶ ግርማ ካሣ ቀልድ ጨምሯል!
ነፃነት ዘለቀ – ከአዲስ አበባ
የግርማ ካሣን ጽሑፎች አልፎ አልፎ አነባቸዋለሁ። ሀገር ወዳድ መሆኑን ይጠቁማሉ – ጽሑፎቹ። ታታሪ ሰው ይመስለኛል፤ በጥረቱና በሀገር ፍቅር ስሜቱ እወደዋለሁ። ሁልጊዜ ሳይታክት ይጽፋል። ሳይታክቱ የሚጽፉ ብፁዓንነት የሚበዛባቸው ቢሆን ዕድለኞች ግን ናቸው። ብዙዎቻችን እየደከመን መጻፍ ቀርቶ ማንበባችንንም እያቆምን በምንገኝበት ሰዓት አዘውትሮ መጻፍ መታደል ነው።