ለጎንደር መርሐ ግብር ተሳታፊዎች


   ጎንደር ላይ በታኅሣሥ 20 ለሚኖረን የ‹‹አራቱ ኃያላን›› መጽሐፍ መርሐ ግብር የተመረጠው 
ታየ በላይ ሆቴል አዳራሽ ነበር፡፡ 
ነገር ግን ከጎንደር ከተማና አካባቢው (ከደብረ ማርቆስ፣ ባሕርዳር፣ ደብረ ታቦር፣ አዲስ ዘመን፣ እስቴና ሌሎችም) በመርሐ ግሩ ላይ ለመሳተፍ የተመዘገቡት ታዳሚዎች ቁጥር ከአዳራሹ ዐቅም በላይ በመሆኑ አዳራሽ ለመቀየር ተገደናል፡፡
በዚህም መሠረት የጎንደር ከተማ አስተዳደር ባሕልና ቱሪዝም ቢሮ ባደረገልን ድጋፍ መርሐ ግብሩ የሚካሄደው በጎንደር ከተማ ሲኒማ ቤት መሆኑን እንገልጣለን፡፡ በዚሁ አጋጣሚም አስቀድሞ ትብብሩን ላደረገልን ታየ በላይ ሆቴል ላቅ ያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡
ጎንደር ላይ እንገናኝ፡፡