የዩክሬኑ ተቃውሞ

የዩክሬን መንግሥት ከአውሮፓ ህብረት ጋር ልዩ የንግድና የፖለቲካ ትብብር ውል ላለመፈረም በመወሰኑ የተነሳው ተቃውሞ ተጠናክሮ ቀጥሏል።በዋና ከተማይቱ በክዬቭና በሌሎችም ከተሞች አደባባይ የወጡ ተቃዋሚዎች የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ቪክቶር ያኑኮቪችና መንግሥታቸው ሥልጣን እንዲለቁ መጠየቃቸውን ቀጥለዋል።