የኛ ነገር፡ ክፍል 20፤ ሰይፋችንን አጥተነው፤ ሰልፋችንንም ልንቀማ ??

ተክለሚካኤል አበበ (ቶሮንቶ-ካናዳ)

የሳኡዲ ግፍና የኛ ሰልፍ፤

እንደመግቢያ፤ የፋና ነገር

1.         ፋና፤ ኢትዮጵያዊ ካናዳዊት ነች፡፡ ቆንጆ ነች፡፡ እሱዋ እንደምትለው ከሆነ ፖለቲካ አትወድም፡፡ በአባይ ቦንድ ሽያጭና በመሰል የመንግስት መርሀ ግብር ዝግጅቶች ላይ ግን ቀድማ የምትገኝ ጎበዝ ነች፡፡ በውጭ አገር የሚገኙ ተቃዋሚዎች መፈክር ይዘው በኢህአዴግ ላይ ሲሰለፉ ስትመለከት ግን ደምዋ ይፈላል፡፡ ሰሞኑን በዚህ በሳኡዲአረቢያ በሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ላይ የደረሰው ግፍ ስላሳዘናት፤ ሳውዲዎችን ልክ ልካቸውን ልትነግራቸው ቆርጣ ተነስታለች፡፡ ስለዚህም በመጪው አርብ መሰል ጉዋደኞችዋን ይዛ ሰልፍ ልትወጣ ተፍ ተፍ ትላለች፡፡ በፋና እምነት በሳኡዲ በኢትዮጵያዊያን ላይ የደረሰው ሰቆቃ፤ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የሚያገናኘው ምንም ነገር የለም፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …