የሳውዲ ዐረቢያ ፀረ ኢትዮጵያዊነት ዘመቻ

ሜሮን አድማሱ ከኖርዌይ
በመቶ ሺ የሚቆጠሩ ኢትዮጵዊያን በሚኖሩባት ሳውዲ ዐረቢያ በአሁኑ ሰአት በኢትዮጵያዊ ወገኖቻችን ላይ እያደረገችው ያለችው ኢሰብዓዊ ድርጊት ለጆሮ የሚሰቀጥጥ ሲሆን፣ ከአንድ ኃይማኖት አለን ከሚል ሀገር የማይጠበቅ አሳፋሪ ተግባር ነው። በታሪክ እንደሰማነው የነብዩ መሐመድ ተከታዮች ሲሠደዱ ኢትዮጵያ በጊዜው ተቀብላ መኖሪያና ማምለኪያ ቦታ እንዳልሰጠቻቸው ሁሉ፤ ዛሬ ግን በኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችን ላይ እያደረሰችባቸው ያለው ስቃይና እንግልት ውለታ በይነቷን ያሳያል።