ለሸገር ልጆች፦፦፦
ለሸገር ልጆች፦፦፦
የድሮ አራዶች እነ ድንጋይ ኳሱ
ቦርቸሌን ከርቸሌን በደንብ ያዳረሱ።
ለወሬ ነጋሪ ካሉ የተረፉ፧
ምን አለ ቢያወጉን፧ምን አለ ቢጽፉ፧
ያዲሳባ ልጆች አብሮ አደጎቼ፣
በናፍቆት ባዘኑ እያነቡ አይኖቼ።
ድንገት ሣናስበው እንደተለያየን፣
በሞያሌ ሾልከን በቦሌ እንገባለን፣
አይቀርም አንድ ቀን፦እናወራዋለን፣
በአመቺው ዘዴ እንተርከዋለን፣
ዕድሜና ጤናውን አምላክ ካልነፈገን።፧
ሁል ግዜ ድሪሜ፣
የዘወትር ህልሜ፣
እንዳይነፍገን ዕድሜ።
እስከምንገናኝ በአካል በዐይነ ስጋ፣
ፌስ ቡክ ያገናኘን እርሱም እስኪዘጋ።
*ድንገት ለተለያየነው አብሮ አደጎቼና ወዳጆቼ ሁሉ መታሠቢያ ተፃፈ።
ተዱ ዘአራዳ ከዩጋንዳ