የሁለት ኢትዮጵያውያን ሁለት አንቀጽ ወግ እና እኔ
አቤ ቶኪቻው
ዳዊት ከበደ እና ተስፋሁን ጫመዳ
ተስፋሁን ጫመዳ የተባለ አንድ ወጣት ኢትዮጵያዊ ነበር። የገዢው ግንባር ኢህአዴግ ነገረ ሥራ አልመችህ ቢለው በተለያየ አጋጣሚ “ተው!” ማለት ጀመረ። ኢህአዴግዬ ግን ተው ባይ አይወድምና በክፉ ዓይኑ ተመለከተው። ይሄኔ ተስፋሁን የሚመጣበትን ጦስ ሸሽቶ መጪው ጊዜ መልካም እንደሚሆን ተስፋ አድርጎ ‘እስኪያልፍ ያለፋል’ ብሎ ሀገሩን ትቶ ተሰደደ።