አፍሪካ ከአይሲሲ ጋር ያላት ግንኙነት
አረንጓዴ – የሮማ ደንብን ስምምነት ፈርመው በፓርላማዎቻቸው ያፀደቁ፤ ቢጫ – የሮማን ደንብ የፈረሙ ግን በፓርላማዎቻቸው ያላፀደቁ፤ ቀይ – የሮማን ደንብ ያልፈረሙና የአይሲሲ አባል ያልሆኑ
አፍሪካ ከአይሲሲ ጋር ያላት ግንኙነት
ሥራ ላይ ያሉ የሃገሮች መሪዎች እንዳይከሰሱ የሚያደርግ ከለላ ዓለምአቀፉ የወንጀል ችሎት – አይሲሲ እንዲሰጣቸውና በኬንያ መሪዎች ላይ የተከፈተው ክስም ላልተወሰነ ጊዜ እንዲዘገይ እንዲደረግም የአፍሪካ ሕብረት ሰሞኑን ጠይቋል፡፡
መሪዎቹ ባለፈው ቅዳሜ፣ ጥቅምት 2/2006 ዓ.ም አዲስ አበባ ላይ ባደረጉት ስብሰባ ጉዳዩን ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሚያቀርብና የሚከታተለ ኮሚቴ አቋቁመዋል፡፡
ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም /ፎቶ ፋይል/ በሌላ በኩል ደግሞ ይህ የመሪዎቹ ጥያቄ አግባብነት የሌለው ነው ሲሉ የፖለቲካ ሣይንስ ምሁር እና የሕግ …