ሣልሳይ ወያኔ – በዲ/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል

እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል!

Screen Shot 2013-09-15 at 4.20.02 PM

ሣልሳይ ወያኔ

በዲ/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል አዘጋጅነት የሚቀርብ በሙከራ የሚገኝ ገጽ ሲሆን በዚህ የመወያያና የመመካከሪያ መድረክ ኃይማኖታዊ፣ ሀገራዊ፣ ማህበራዊና ወቅታዊ እንዲሁም በሰብአዊ መብት ዙሪያ ለሚነሱ ጥያቄዎች ዲ/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል ከሥነ መለኮት ዕይታ ወንጌላዊ፣ ምሁራዊና ሙያዊ ትንተናና ሐተታ የሚሰጡበት ገጽ ነው።

ሣልሳይ ወያኔ

  • ሸቀጥ፣ አድርባነትና ወገበነጭነት የሚቸነከሩበት፥ 
  • ጽድቅና እውነት የሚነገረበት፥
  • አመጻ፣ ጦርነትና ሁከት የሚወገዝበት፥
  • ፍቅር፣ እምነትና ተስፋ የሚሰበክበት፥ 
  • ሰላም፣ አንድነትና ህብረት የሚታወጅበት፥
  • ዜጎች በዜግነታቸው ብቻ በእኩልነት የሚገለገሉበት፥
  • የተለየ ሃሳብ ያለው የሚስተናገድበትና ሃሳብ ለሃስብ ብቻ የሚፋጭበት፥  
  • ራስዎን በነገሮች ሚዛናዊነትና ፍትሐዊነት የሚያዩበት፥ 
  • ነውራሞች፣ ጸብ ጫሪዎችና እሳት አንዳዲዎች የሚጋለጡበት፥
  • የአደጋ ጣዮች መሰሪና አጥፊ አጀንዳ የሚገለጥበት፥
  • እውነት የምትሸጥበት ሳይሆን የምትገዛበት፥
  • “ደጋፊ” አልያም “ተቃዋሚ” የሚል መታወቂያ የሌለው ለሕዝብ የቆመ ሕዝባዊ ገጽ ነው።

የሣልሳይ ወያኔ ድረ ገጹ አዘጋጅ ሲያስቡ ከምንም በላይ ግለሰቡ የሚቆረጥ ፔሮል የሚከስር ሱቅ እንደሌላቸው አይዘንጉ። ከዚህም የተነሳ አዘጋጁ እውነት በእውነትነቱ ብቻ በፍቅር የመግለጥ የመናገር የመመስከርና የማስተማር ችግር የላቸውምና ያዩትና የሰሙት ነፍስ የሚያሳርፍ የምስራች ዜና ለቤተ ዘመድ ለወዳጅና ለጎሮቤት [http://salsaywoyane.wordpress.com/] በመጠቆም፣ በመናገር፣ በማስተላለፍና በማካፈል  ዜግነታዊ ግዴታዎ ይወጡ!

ዲ/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል

http://salsaywoyane.wordpress.com/