የአሜሪካ ምርጫ መጻኢ ዕጣ ፈንታቸውን ጥያቄ ውስጥ የከተተው አፍሪካውያን ስደተኞች

በአሜሪካ ምርጫ የቅስቀሳ ዘመቻ ወቅት ስደት ዋነኛ ጉዳይ ነው። ሁለቱም ዕጩ ፕሬዚዳንቶች የዲሞክራቷ ካማላ ሃሪስም ሆኑ የሪፐብሊካኑ ዶናልድ ትራምፕ በድንበር በኩል የሚገቡ ስደተኞችን ማስቆም ዋና ተግባራቸው እንደሚሆን ቃል ገብተዋል። በዚህም ምክንያት አፍሪካውያን ጥገኝነት ጠያቂዎች ሕዝቡ ፊቱን ሊያዞርብን ይችላል የሚል ስጋት ገብቷቸዋል።