ጎንደር በሕዝብ ማዕበል ተጥለቅልቃለች!ፎቶዎችን ይመልከቱ

ምንም እንኳ ራዲዮ ፋናና የሕወሃት ካድሬዎች የሕዝቡን ሕገ መንግስታዊ መብት ለማፈን ቢሯሯጡ ሕዝቡ ግን መብቱን ከማስከበር ወደ ኋላ አላለን። የፍርሃት ቀንበርን ሰባብሮ ጥሎ ከአራቱም ማእዘናት ወደ አደባባይ በመምጣት ፍጹም ጨዋነት በተላበሰ ሁኔታ ድምጹን እያሰማ ነው። ሕወሃቶች ይህን ህዝብ የሻእቢያ አሸከር እያሉ ሲሳደቡባ ሲያጥላሉት እንደነበረ ይታወቃል። አስር ጊዜ “ሕግ፣ ስርዓት..” እያሉ ለሕግና ለሰላም የቆሞ ለመምሰል የሞከሩበት ሁኔታ አለ። ሕዝቡ ግን ሕግ አክባሪ ሰላማዊ መሆኑን በይፋ እያስመሰከረ ነው።እስከ አሁን ባለው የሰልፍ ሂደት ፍጹም ስነ ስርዓት የነበረው ሲሆን፣ ምንም አይነት ችግር አልተፈጠረም።

ሰልፈኞቹ በሚያስደንቅ ሁኔታ የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ ከፍ አድርጎ በማውለብለብ የአንድነትን ደቁል ደዉለዋል።

138826

13686494_10157500545625354_4456691172760173583_n

13876395_10157500545630354_3984602988133288247_n

Gondar-protest-July-31-2016

13900394_1172695232752529_754692305_n

121