የሽመልስ ከማል የፖለቲካ ጥገኝነት መጠየቅ እውነት ከሆነ …ብዙ እናያለን ብዙ እንሰማለን
የባለስልጣኖች መክዳት የተቃዋሚዎች የትግል ውጤት አንዱ አካል ነው:: በኢትዮጵያ የፍትህ ሂደት ውስጥ ከፍተኛ ተባሳ ጥለው ሕዝብን አንገቱን በማስደፋት ለለቅሶ የዳረገው የቀድሞ ዳኛ የዛሬው ባለስልጣን አቶ ሽመልስ ከማል ወደ አሜሪካ በግል ተጉዞ የፖለቲካ ጥገኝነት ጠየቅ የሚሉ ጭምጭምታዎች መሰማት ከተጠያቂነት ለመዳን የሚደረግ ሩጫ ,,,, እርግጥ ለትግሉ መረጃ በማሰባሰብ ረገድ ሽመልስ ከማል ሊረዳ ይችል ይሆናል ሆኖም ጎን ለጎን የፍትህ ስርአቱን በማኮላቸት እና በማበላሸት በኮሚኒኬሽን ስራ በሃሰት ሕዝብን ለማዘናጋት በፕሮፓጋንዳ በማጭበርበር ተግባራቸው ከተተያቂነት አይድኑም:: አሜሪካ የምትባል አገር በፈቃዷ የቆሻሾች ማጠራቀሚያ ሆነች?
በእኔ እይታ የባለስልጣኖች መክዳት የተቃዋሚዎች የትግል ውጤት አንዱ አካል ነው::ተቃዋሚዎች የወያኔን አምባገነንነት በገሃድ ማጋለጣቸው ለስር አት መፍረክረክ አስታውጾ አለው::የአቶ ሽመልስ ከማል መክዳት እውነት ሆኖ ከተገኘ ለትግሉ የመረጃ ፍሰውት በጣም ጠቃሚ ነው::እንደ ብስራት አማረ ያሉ ሃገር ቤት የሚመላለሱ የወያኔ ሙቀኞች ወንጀል ሰርተው በወንጀል ታጥበው በአሜሪካ እየኖሩ ነው::ሽመልስ በስርአቱ ውስጥ የሚፈጸሙ ወንጀሎች የሕወሓት ምንጫቸውን ማወቅም አዛዦችንም መለየቱ ለማወቅ አስፈላጊ ሰው ነው::የባለስልጣናት መክዳት የስርአቱን መበስበስ ያመለክታል::ያም ሆነ ያም ዋናው ለትግሉ የሚጠቅሙ መረጃዎችን ማግኘት ነው::ስለዚህ ጉዳዩን በሰከነ መልኩ ማየት ነው: