አንድነት ፓርቲን ለማፍረስ የተወጠነው ሴራ በዶክመንተሪ ፊልም ተቀናበረ::
አንድነት ፓርቲን ለማፍረስ የተወጠነው ሴራ በዶክመንተሪ ፊልም ተቀናበረ::
በነሀብታሙ አያሌው እና የአንድነት አባላት ላይ ለመመስከር ስምምነት ተደርሷል::
የኢህአዴግ ሰርጎገብ የሆኑትና አንድነትን ለማፍረስ የሚንቀሳቀሱት(በትግስቱ አወሉ የሚመሩት) አካላት በምርጫ ቦርድና ጽ/ቤት ለብሄራዊ ደህንነት አባላት በቪዲዮ በሰጡት የሃሰት ምስክርነት አንድነት ፓርቲ በግንቦት7 ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦለት እየሰራ ነው የሚል መረጃ መስጣታቸው ታወቀ፡፡ ሰርጎገቦቹ የአንድነት አባላት በሆኑትና አሁን በእስር ላይ በሚገኙት እነሀብታሙ አያሌው ላይም የሀሰት ምስክርነት ለመስጠት ተስማምተዋል፡፡
ዳንኤል ሙላት፤ኤዶም ሰይፉ፤ደረጀ ጣሰው እና ገዛሀኝ ንጉሴ በነሀብታሙ አያሌው እና ዳንኤል ሺበሺ ላይ ለተመሰረተው ክስ የአቃቤ ህግ ምስክር ሆነው ለመቅረብ የውል ስምምነት ፊርማቸውን በትላንትናው እለት በአራዳ ክፍለ ከተማ ወጣቶች ሊግ ቢሮ አኖሩ፡፡ፓርቲውም ለነሱ ተላልፎ እንደሚሰጣቸው አልያም ሊዘጋ እንደሚችል ቃል ተገብቶላቸዋል ፡፡
