ደሴ በበራሪ ወረቀት አሸብርቃ አደረች::

እንቢኝ ለመብቴ እንታገላለን ያሉት የደሴ ሙስሊሞች ደሴን በበራሪ ወረቀት አሸብርቀዋት አደሩ::

መንግስት የደሴን ሙስሊም በሀይል ቀጥቅጨ ተቆጣጥሬዋለሁ ብልም ፉከራውን መና የሚያሰቀር ሁኟን:: በተያያዘ ዜናም በዚሁ ድርጊት የተደናገጡት የመንግስት ደህንነቶች እና አቀንቃኝ ካድሬወች በሌሊቱ ተነስተው በስራ ተጠምደው እንዳደሩም ለማወቅ ተችሏል::

በበራሪ ወረቀቱ ላይ ጎልተው ከሚታዩት መፈክሮች መካከል 1.ኮሚቴወቻችን ወንጀለኝ አይደሉም ንፁህ ናቸው ይፈቱልን 2.መንግስት በሙስሊም እና ክሪስቲያን መካከል ግጭት ለመፍጠር ድራማ እየሰራ በ Etv የሚያቀርበው ፕሮፓጋንዳ ይቁም 3.አሸባሪ አይደለንም 4.ትግሉ ይቀጥላል 5.ድምዻችን ይሰማ እና ኮሚቴው በፍጥንነ ትይፈታ አለያ አንደራደርም የሚሉት ይገኙበታል::

የደሴ ሙስሊም በኮሚቴወቹ ላይ መንግስት የጥፋት እጁን ከሰነዘረ እንደማይደራደሩ ዛሬ ተበትኖ ባደረው 50000 ሺ በራሪ ወረቀት አስረግጦ አሳስቧል:: ሲቀጥልም ዱላ እስር እና ግድያ የማይበግረው የደሴ ሙስሊም ትግሉ እስከ ድላችን ድረስነው በቀይ ይሰመርበት ሲሉ አሳስበዋL:: ድል ፍትህ ለተጠማው ሙስሊም አላህ አክበር!