የተስፋዬ ገ/ኣብ ነገር ስራ – የኦሮሞ ሚዲያ ኔትወርክ (OMN) አደጋ

ተስፋዬ ገ/ኣብ በየሄደበት ሁሉ መርዝ መርጨቱን ኣያቆምም፡፡ በቅርቡ የኦሮሞ ልጅነትን (ፎርጅድ) አግኝቻለሁ በማለት ተናግሮ ሳይጨርስ ነጻ ሆኖ ይንቀሳቀስ የነበረዉን የኦሮሞ ሚዲያ ኔትወርክ (OMN) አደጋ ውስጥ ጨምሮታል፡፡ OMN ከተመሰረተ እንኳ አንድ አመት ሳይደፍን ይኸዉ ከሁለት መከፈሉን የተለያዩ ሚዲያዎች እየነገሩን ነዉ፡፡
ይህ የሚዲያ ተቋም የሰዉ ሀይል ችግር ኖሮበት አይመስለኝም፡፡ እነ በፈቃዱ ሞረዳ ከዚህም በላይ መስራት የሚችሉ ሰዎች ናቸዉ፡፡ በፈቃዱ በተደጋጋሚ ባደረጋቸዉ ቃለ መጠይቆች ወገንተኝነትን የማይፈልግ ፍጹም የጋዜጠኛነት ሙያ የሰረጸዉ ሰዉ መሆኑን አስመስክሯል፡፡
በእኔ እምነት ችግሩ ተስፋዬን ወደ ህብረታቸዉ ማስጠጋታቸዉ ነዉ፡፡ ተስፋዬ ገብረ አብ በማንኛዉም መንገድ ለኦሮሞም ሆነ ለሌላዉ ኢትዮጵያዊ ህብት እንደማይፈልግ እነ በፈቃዱና ሌሎችም የተረዱት አልመሰለኝም፡፡ እናም ይኸዉ አንድ አመት ሳይደፍን ከጆሀር መሀመድ ጽንፈኝነት ጋር ተጨማምሮ ሚዲያዉን ህልዉና ተፈታተነዉ፡፡
viewtopic.php?f=2&t=90612