የአማራ ንቅናቄ ሻእቢያ አመራሮቼን አግቶ ሰውሮብኛል ሲል በድጋሚ ከሰሰ(ሙሉ መግለጫውን ያንብቡ)

የአማራ ንቅናቄ ሻእቢያ አመራሮቼን አግቶ ሰውሮብኛል ሲል በድጋሚ ከሰሰ(ሙሉ መግለጫውን ያንብቡ)
‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎Eritrea‬ ‪#‎AmaraForce‬ ‪#‎Ginbot7‬ ‪#‎EPPF‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬
ኤርትራ ውስጥ ተቀምጦ በትጥቅ ትግል ነጻነት ይገኛል ብሎ ስለማያስብ ወሳኝ ሃይሉን ከኤርትራ ያስወጣው አማራ ንቅናቄከማንም አስመራ ከመሸገ ድርጅት ጋር ውህደትም ሆነ ትብብር አለመፍጠሩን እና ከሻእቢያ ቁጥር ውጪ ካልወጣን በስተቀር ውህደትም ይሁን አስመራ ተቀምጦ የኢትዮጵያ ህዝብ ነጻነት አይታሰብም ሲል ተደምጧል::
የኤርትራ መንግስት በህገወጥ ሁኔታ ያገታቸውን እና የስወራቸውን ታጋዮቻችንን በአስቸኳይ እንዲለቅ ሲል የአማራ ንቅናቄ ጠየቀ:: የአማራ ንቅናቄ የሚከተሉት በሻእቢያ አመራሮቹ ታፍነው ተወስደዋል ሲል በድጋሚ አስታወቀ::በዚህም መሰረት:
1ኛ – ታጋይ ዳዊት ተሰማ የድርጅቱ ም/ሊቀመንበር እና የፖለቲካ ጉዳዮች ሃላፊ
2ኛ – ታጋይ መላኩ ውብነህ (ሳሚ) የድርጅቱ የትምህርት እና ስልጠና ሃላፊ
3ኛ – ታጋይ ጌትነት አድማሱ (ጃናሞራ) የሻምበል አዛዥ
4ኛ – ታጋይ አስማማው ሙሃባው የሎጀስቲክ እና አቅርቦት ሃላፊ
5ኛ – ታጋይ መሳይ ጥላሁን (ዳሞት) የሻምበል አዛዥ
Image

Image