በ9ኙ ፓርቲዎች ተጠርቶ የነበረው የአደባባይ ስብሰባ ፖሊስ በኃይል በትኖታል! photos

ፖሊስ ህዝቡን ለመበተን እየጣረ ነው፡፡የስብሰባው አዘጋጆች አንሄድም ብለው ሜዳው ላይ ይገኛሉ፡፡
#Ethiopia #Blueparty #Election2007 #NegereEthiopia #MinilikSalsawi
9ኙ ፓርቲዎች የጠሩት የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በኃይል ተበተበ
ዛሬ ህዳር 7/2007 ዓ.ም 9ኙ ፓርቲዎች በትብብር የጠሩት የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በፖሊስና በደህንነት ኃይሎች ተበትኗል፡፡ ፓርቲዎቹ ለሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል ያሳወቁ ሲሆን የፓርቲዎቹ አመራሮች ለፖሊስና ደህንነቶች ቢያሳዩም ‹‹የምናውቀው ነገር የለም፣ እኛ ታዘን ነው፡፡ ከፈለጋችሁ አለቆቻችን ሂዳችሁ አናግሩ፡፡›› በማለት ለስብሰባው የተዘጋጁትን ቁሳቁሶች ስብሰባው ሊደረግበት ከታሰበው ሜዳ እንዲነሱ አድርገዋል፡፡
የፓርቲዎቹ አመራሮችና በስብሰባው ለመሳተፍ ወደቦታው ያቀኑ አካላት ለማሳመን ጥረት ቢያደርጉም ፖሊስ ግን ህዝቡን በኃይል በትኗል፡፡
ፖሊሶች የፓርቲውን አመራሮች በማስፈራራት ላይ ይገኛሉ #የቤለዬሩ_ሰልፍ Morning Update
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
ስብሰባው እንዳይደረግ የሚከለክሉት ፖሊሶች ለምን ትከለክላላችሁ በሚል ለሚነሳው ጥያቄ እነሱ የሚሰጡት መልስ አናውቅም፣ ታዘን ነው የሚል ነው፡፡ የፓርቲዎቹ አመራሮች ስብሰባው እውቅያ ያገኘበትን ደብዳቤ ቢያሳዩዋቸውም እኛ ስለጉዳዩ አናውቅም ነው ያሉት፡፡
ፖሊስ ህዝቡን ለመበተን እየጣረ ነው፡፡ፖሊስ የአደባባይ ስብሰባ በኃይል ለማገድ እየወጣ ነው፡፡ ሞንታርቮና ጀኔሬተር የመሳሰሉትን ቁሳቁሶች በኃይል አንስተዋል፡፡ የስብሰባው አዘጋጆች አንሄድም ብለው ሜዳው ላይ ይገኛሉ፡፡ ለስብሰባው የመጣው ህዝብ ሁኔታውን ለመቅረጽ እንዳይሞክር እየጠደረገ ነው፡፡ በአንጻሩ ግን ደህንነቶች ህዝቡን እየቀረጹ ይገኛሉ፡፡