የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል ተብየውም የምልመላ ክፍል ሃላፊ ከነበረው ቴዎድሮስ ስዩም ጋር የተደርገ ውይይት
ቴዎድሮስ በደቡብ አፍሪካ ከ10 ዓመት በላይ የኖረ፣ የራሱን የተደላደለ ኑሮ ይመራ የነበረ፣ ነገር ግን በነ አንዳርጋቸውና ብርሃኑ እንደሌሎች ጓደኞቹ ለአመራር ስልጠና በኤርትራ በኩል ወደ አውሮፓ ትላካላችሁ በሚልና ሌላም ሌላም የእውሸት ክምር ተታሎ ወደ ኤርትራ የሄደ፤ ልክ ኤርትራ እንደገቡ የውሸቱን ክምር ለማወቅ ጊዜ አልወሰደበትም። ከሌሎች ጓደኞቹ ጋር በመሆን ከብርሃኑ ነጋ ጋር ባደረገው የስካይፕ ውይይት ብርሃኑ እራሱን ነጻ ለማድረግ እኔ የማውቀው ነገር የለም፤ አንዳርጋቸው ብቻ ነው የሚያውቀው በሚለው አነጋገሩ ድርጅቱ ባለቤት የሌለውና የደረሰበትንም የውድቀት ደረጃ ተረድቶ ለእስር ከመዳረጉ በፊት አስቀድሞ አካሄዳቸውን ማየት የቻለና ሁኔታዎችን አመቻችቶ የወጣ ወጣት ነው። የህዝባዊ ሃይል ተብየውም የምልመላ ክፍል ሃላፊ የነበረ ሲሆን በአባላት ለህዝባዊ ሐይሉ ምክትል አዛዥነትም ተመርጦ ነበር። ቴዎድሮስ ከኤርትራ እንደወጣ ባለፈው አመት “በኛ ይብቃ” በሚል ርእስ ህዝብን ያስደመመ ጽሁፍ በመጻፍ እኩይ ምግባራቸውን ያጋለጠ ፋና ወጊ ወንድማችን ነው። ቴዎድሮስን ተደብቆ ከሚኖርበት አግኝተን አነጋግረነዋል ውይይቱን ተከታተሉ፤
loading … [audio]
Or click here: http://www.ginbot7d.org/audio/TewdrosMinilik.mp3