የመርካቶው ጆኒያ ተራ ቃጦሎ ነጋዴዎች ንብረታቸው መቃጠሉ ሳያንስ በዱላ ተደብድበዋል ፡፡
እሳት አደጋ ሰራቶኞች 50000 ብር ግቦ ተቀብለዋል ::
ከቀኑ በስምንት ሰአት የጀመረ እስከ ምሽቱ ሶስት ሰአት ድረስ አልተቆጣተሩትም ::
የእሳቱን ጪስ መላው የአዲስ አበባ ነዋሪ በያለበት በሀዘን ሲመለከተው ነጋዴዎች ንብረታቸው መቃጠሉ ሳያንስ በዱላ ተደብድበዋል ፡፡
የእሳት አደጋው መንስኤ በገለልተኝ አካላት አስኪጣራ ምንም ከማለት መቆጠቡ አስፈላጊ ቢሆንም ሀላፊነት የሚሰማው ለህዝብ መሰዋትመት የሚከፍል የድንገተኝ አደጋዎችን የሚቆጣጠር የመንግስት አካል አለሞኖሩ ህብረተሰባችንን በጣሙን ያሣዘነ ሆኖ አልፏል ፡፡ የእሳትና ድንገተኝ አደጋ ሰራተኞች እሳቱ ልክ ከቀኑ በ 8 ሰአት እንደተቀሰቀሰ መረጃው ቢደርሳቸውም ቦታው የደረሱት 9 ሰአት ላይ መሆኑ ያበሳጫቸው የአካባቢው ነዳዴዎች እቃቸውን ለማሸሽ በሚያደርጉት ትግል ብዙዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል::
በተጨማሪም በቦታው ቀደም ብለው የደረሱ የፌደራል ፖሊሶች እሳቱን ለማጥፋት ህብረተሰቡን ከማስተባበርና ይበልጥ ጉዳት እንዳያደርስ ከመከላከል ይልቅ የአካባቢውን ነጋዴዎችና
እሳቱን ለማጥፋት የሚረበረቡትን በዱላ እየደበደቡ ሲያባርሩ ተስተውለዋል ፡፡ ከዚህ በባሰ መንግስት የለም ወይ የሚያስብለው የእሳትና የድንገተኛ አደጋ ሰራተኞች እቦታው ደርስው መኪናቸው ውስጥ
ዝም ብለው ሲቀመጡ በንዴት ንብረጃቸውን ለማሸሽ ተንደርድረው ወደሱቃቸው የገቡትን ነጋዴዎች በውሃ ገፍትረው የጣሉዋቸው ሲሆን እነዘህም ነጋዴዎች በተክላሀይማኖት ሆስፒታል በህክምና ላይ ይገኛሉ ፡፡
ብር ካልተሰጣቸው እንደማያጠፉ የተረዱት 2 ነጋዴዎች ሀምሳ ሺህ ብር አዋጥተው እንደሰጦቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡ ለአደጋው መባባስ በመጀመሪያ ደረጃ ተጠያቂው የመንግስት አካላት መሆናቸው የአደባባይ ሚስጥር ነው ፡፡ስምንት ሰአት ሙሉ መርካቶ በቃጠሎ ውስጥ የነበረች ሲሆን የሁለት ብሎኮች ንብረቶችም ሙሉ በሙሉ ወድመዋል ፡፡የእሳቱን ጪስ መላው የአዲስ አበባ ነዋሪ በያለበት በሀዘን ሲመለከተው አምሽቷል፡፡ እሳቱን ማቆም የተቻለው ከምሽቱ ሶስት ሰአት ላይ መሆኑንም
አየይን እማኞች አክለው ገልጸዋል ፡፡